"ጠንከር ያለ ሃሳብን፣ ድንቅ ገለጻን እና ጥልቅ ሀዘንን አዋዉጦ በአንድ ያሰረ ፅሁፍ ነው:: ገፀ ባህሪው እንደተጋደመ ሕይወት በአሱ በኩል አንዴት አንደ እንደተገለጠች የሚተርከልንን ታሪከ ግንባራችንን ገምደን እንደተቀመጥን እንዘልቀዋለን፡፡ አህመድ ሁስ በዚህ መፅሐፉ፥ በየትኛውም ዓለም አቀፍ የስነ ፅሁፍ ውድድር ቢቀርብ፥ ፊት ከይመልሱበትም ኣንገት ከይቀልሱበትም ብዬ አምናለሁ፡፡ ደራሲው በዚህ መፅሐፍ ያሸከመንንና አአምሮአችንን የወጠረዉን ሃሳብና ሀዘን ለመቋቋም አንደ ስም የለሹ ገጸ ባህርይ መብጫ ምላጭ ቀድመን ካላዘጋጀን ለተገመደው ግንባራችን "ወዮ ድንቅ ገለንን ጥልቅ ሀዘንን አዋዉጦ በአንድ ያሰረ ፅሁፍ ነው:: ገፀ ባህሪው እንደተጋደመ ሕይወት በአሱ በኩል አንዴት አንደ እንደተገለጠች የሚተርከልንን ታሪከ ግንባራችንን ገምደን እንደተቀመጥን እንዘልቀዋለን፡፡
"አህመድ ሁስ በዚህ መፅሐፉ፥ በየትኛውም ዓለም አቀፍ የስነ ፅሁፍ ውድድርቢቀርብ ፊት ከይመልሱበትም ኣንገት ከይቀልሱበትም ብዬ አምናለሁ፡፡ ደራሲው በዚህ መፅሐፍ ያሸከመንንና አአምሮአችንን የወጠረዉን ሃሳብና ሀዘን ለመቋቋም አንደ ስም የለሹ ገጸ ባህርይ መብጫ ምላጭ ቀድመን ካላዘጋጀን ለተገመደው ግንባራችን "ወዮ" ነው፡፡
ይቺን ምጥን መፅሐፍ ብታነቡ ታተርፋላችሁ ስል በኩራት ነው።"
ትዕግስት ታፈረ ሞላ (ደራሲ)
___________________
"በዚህ ዘመን ሞት በጉያችን ይዘነው የምንዞረው ሆኗል። እንኳንስ ወደአለበት ሂደንበት፥ አንደጥላ ስር ስራችንን ይከተለናል፡፡ ወጣቱ ስሜተ-ስስ አየሆነ ነው᎓᎓ ወደ ሞት የሚወስደውን ጎዳና ከመላከተነው ይቅርና ቅያሱ ሁሉ ወደ ሞት ኣድራሽ ሆኗል።
"ስለሆነም ይህን መፅሐፍ ማንኛውም አይነት ስነልቦናዊ ችግር፣ ከፍተኛ ድብርትና ጭንቀት ውስጥ ያለ ሰው እንዳያነበው ይመከራል።"
ሽመልስ ይርጋ (ዶ/ር)